ቦሌ ክፍለ ከተማ አልፋ መስማት የተሳናቸው 2ኛ ደረጃ ልዩ ት/ቤት የተለያዩ እቃዎችን መግዛት ይፈልጋል – test3.diretenders.com

ቦሌ ክፍለ ከተማ አልፋ መስማት የተሳናቸው 2ኛ ደረጃ ልዩ ት/ቤት የተለያዩ እቃዎችን መግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen (Aug 13, 2026)

በጨረታ ለሚገዙ ዕቃዎች ለተጫራቾች የ1ኛ ዙር
የጨረታ መመሪያ ሰነድ የጨረታ ቁጥር 01/2018

በአገር ውስጥ ለሚፈጸሙ እቃዎችና ተዛማጅ አገልግሎቶች የሚውል የሚገዙ እቃዎች የአላቂ የቢሮ እቃዎች፣ ቋሚ እቃዎች፣ አላቂ የት/ት እቃዎች፣ የደንብ ልብስ፣ የእስፖርት እቃዎች የላብራቶሪ እቃዎች 1 የጽዳት እቃዎችና የተለያዩ ቀለሞች፡-

  • በመጀመሪያ ደረጃ ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ለመግዛት የሚችሉት በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዝጋቢ የምስክር ወረቀት ያላቸው ወይንም ማቅረብ የሚችሉ ብቻ ናቸው።
  • ተጫራቾች የሚያቀርቡት የማወዳደሪያ ሂሳብ የዕቃው አይነት የተመረተበት ዓመተ ምህረት የአገልግሎት ዘመን ማብቂያ የአምራቹ ስም ያካተተ መሆን አለበት።
  • ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ቫትን ጨምሮ መሆን ይኖርበታል።
  • ማንኛውም ተጫራቾች በየዘርፉ ንግድ ፈቃድ መኖር አለበት።
  • ማንኛውም ተጫራቾች ዋናው የጨረታ ሰነድ ላይ በተጫራቹ የሚሞሉትን በመሙላት እያንዳንዱ ገጽ ላይ የድርጅቱን ማህተም በማኖር ሳይጨምር ሳይቀንስ መመለስ ይኖርበታል።
  • የጨረታ ፖስታ ዋናና ኮፒ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ መቅረብ አለበት። እነዚህም ሰነዶች የጨረታ አቅራቢው ድርጅት ወይም ህጋዊ ውክልና ባለው አካል መፈረም አለባቸው።
  • ተጫራቾች የእቃዎች ናሙና ከየአይነቱ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤ የጨረታው ውጤት ከታወቀ በኋላ የቀረቡት ናሙናዎች
  • ለተሸናፊዎች ሲመለሱ የአሸናፈው ተጫራቾች ግን ናሙናዎች አይመለስም አንድ ተብሎ ይቆጠርለታል።
  • ግዢ ፈፃሚው አካል አሸናፊ ተጫራቾች በሚመረጡበት ጊዜ የገዛውን እቃ እንደአስፊላጊነቱ እስከ 20% ለመቀነስ ወይም ለመጨመር ይችላል።
  • የዘመኑን ግብር ስለመክፈሎ የሚያሳይ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ ብቻ።
  • የጨረታ ሰነድ መግዛት የሚፈልጉ ተጫራቾች ዘወትር በስራ ሰዓት ከ2፡30-9፡00 ይሆናል። ይህ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ አንስቶ አስከ ለ10/አስር/የስራ ቀናት አየር ላይ ይቆያል፤ በ10ኛው ቀን 9፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በ11ኛው ቀን በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
  • ተጫራቾች በሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ወይም ሰነድ ላይ ስማቸውን ፊርማቸውን አድራሻቸውን እንዲሁም ስልክ ቁጥራቸውን ማስፈር አለባቸው።
  • ተጫራቾች በጨረታው ሰነድ ላይ የማብራሪያ ወይም ማሻሻል አለበት የሚሉ ጥያቄ ካላቸው የጨረታ ሰነዱ የመክፈቻ ጊዜ ሁለት ቀናት እስከሚቀረው ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • ግዥ ፈፃሚ አካል ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  • የሰነዱ መሸጫ በሎት ዋጋ 100 መቶ/ ብር ብቻ።
  • ማንኛውም ተጫራች ባስገባው ጨረታ ሲፒኦ ማስያዣ ዋጋ ሎት1፡ 10,000 ለኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ሎት2፣ 10,000 ለፈርኒቸር እቃዎች ሎት3፡2000 ለትምህርት እቃዎች ሎት4፡1000 ለጽዳት እቃዎች፣ ሎት 5፣ 1000 ለተለያዩ ቀለሞች ሎት-6፣ 3000፤ ሌሎች እቃዎች ሎት 7፣ 3000 የእስፖርት እቃዎች፣ ሎት 8፣ 1000 የደንብ ልብስ ሎት 9፣ 4000 ለላቦራቶሪ እቃዎች ሲሆኑ ሰነዱ በራሱ አንድ የጨረታ መመሪያ መሆኑን ተጫራቾች መረዳት ይኖርባቸዋል።
  • ከላይ የተዘረዘሩ አንድም ነገር እንኳን የማያሟላ ከውድድሩ ውጭ ይሆናል።
  • የርክክብ ቦታ በት/ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ እቃው ለንብረት ክፍል ካስገባና ጥራቱ ከተረጋገጠ በኋላ ክፍያው ይፈጸማል።
  • አድራሻ :- አሰፋ መስማት የተሳናቸው ልዩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ቦሌ ክፍስ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ስሙ ኢንስቲትዩት ጀርባ 500 ሜትር ገባ ብሎ ነው።

ቦሌ ክፍለ ከተማ አልፋ መስማት የተሳናቸው 2ኛ ደረጃ ልዩ ት/ቤት