ወገን የሕጻናት እና እናቶች መርጃ ድርጅት እ.ኤ.አ 2026 የበጀት ዓመት ሒሳብ ለማስመርመር ይፈልጋል – test3.diretenders.com

ወገን የሕጻናት እና እናቶች መርጃ ድርጅት እ.ኤ.አ 2026 የበጀት ዓመት ሒሳብ ለማስመርመር ይፈልጋል


Be'kur (Sep 07, 2026)

ግልጽ የጨረታ ማሰታወቂያ

ወገን የሕጻናት እና እናቶች መርጃ ድርጅት በኢፊዲሪ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ኤጀንሲ ፈቃድ ቁጥር 0712 ተመዝግቦ ከመጋቢት 1/2012 ዓ/ም ጀምሮ በሥራ ላይ ያለ ሀገር በቀል ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ነው፡፡

ድርጅታችን እ.ኤ.አ 2026 የበጀት ዓመት ሒሳብ ለማስመርመር (ኦዲት) ስለፈለገ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ የኦዲት ድርጅቶች መወዳደር ይችላሉ፡፡

1. የሙያ ማረጋገጫ ፈቃድ ያላቸው፡፡

2. INPAS የኦዲት አሰራርን የሚተገብር፡፡

3. የፐብሊክ ኦዲተርነት ፈቃድ ያላቸዉ፡፡

4. ከፌደራል ወይም ከክልል ኦዲት መስሪያ ቤት የዚህ በጀት ዓመት የታደሰ ፈቃድ ያላቸው፡፡

5. በኦዲት ብቁ የሥራ ልምድ ባለሙያ ያላቸው፡፡

6. የዘመኑን ግብር ስለመከፈሉ ማረጋገጫ ያላቸው፡፡

7. በበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና ማህበራት ኤጀንሲ በኦዲተርነት የተመዘገቡ፡፡

8. ተወዳዳሪዎች ለአገልግሎቱ የምታስከፍሉትን ዋጋ እና ሥራዉን አጠናቃችሁ የምታስረክቡበትን የቀን ገደብ የሚገልጽ ሰነድ በማያያዝ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉ 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ወደ ቢሮችን በመምጣት ሰነዳችሁን ማስገባት የሚችሉ፡፡

9. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ስልክ ቁጥር 058 111 22 30 ደውለው መረጃ መጠየቅ ይችላሉ፡፡

አድራሻ ፦ ጎንደር ቀበሌ 01
ወገን የሕጻናት እና እናቶች መርጃ ድርጅት


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *