Addis Zemen (Jun 04, 2026)
ያገለገሉ ዕቃዎች ግልፅ የጨረታ ሽያጭ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ በ2018 በጀተ ዓመት በመስሪያ ቤቱ አገልግሎት ሊሰጡ ማይችሉ የተለያዩ የፍሎረሰንት ማቀፊያዎች፣ አምፖሎች፣ ጣውላዎች፣ ወንበሮች፣ ጋዜጣዎች፣ ምንጣፎች፣ መጋረጃዎችና…ወዘተ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ስለሚፈልግ በዘርፉ የተሰማራችሁ ድርጅቶች የእቀዎችንን ዝርዝር የያዘውን ሰነድ በብር 200 ሁለት መቶ በመግዛት እንድትወዳደሩ እንጋብዛለን።
- ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ እና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ሰነድ ማይመለስ 200/ሁለት መቶ ብር በመግዛት ይህ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአስር ተከታታይ /10/ አስር ቀናት ውስጥ በግዥ ንብረት ጠቅላላ አገልግሎት በመገኘት ሰነዱን መግዛት ይችላሉ
- ተጫራቾች በገዙት ሰነድ ላይ ብቻ ዋጋ በመሙላት፣ በማህተም በማረጋገጥ እና በፖስታ በማሸግ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው። የቴክኒካል ሰነድና ፋይናንሻል ሰነድ በማለት ለይተው ማቅረብ ሲኖርባቸው ይህንኑ መረጃ ከገዙት ሰነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ አለባቸው።
- አሸናፊው ተጫራች ውል ከመፈረሙ በፊት በጨረታ ሰነዱ ከተገለፀው አቅርቦት መጠን 25% በላይ መጨመር ወይም መቀነስ ይቻላል።
- ጨረታው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአስር ተከታታይ ቀናት ውስጥ ዋጋ የሞሉበትን ሰነድ በማስገባት በ11ኛው ቀን 3፡00 ሶስት ሰአት ተዘግቶ 3፡30 (ሶስት ተኩል) ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት እለት ይከፈታላል።
- ቢሮው ጨረታው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ ሜክሲኮ ሰነዱ የሚሸጠው ፊሊፕስ ህንፃ አጠገብ ፍትህ ቢሮ ህንፃ ከፌዴራል ፖሊስ ወረድ ብሎ በሚገኘው የመስሪያ ቤቱ ህንፃ 4ኛ ወለል ላይ ይሆናል።
ስልክ 011 515 954
ማሳሰቢያ! ተጫራቾች ዕቃዎቹን በአካል በመገኘት ማየት ይኖርባቸዋል
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ