የአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2019 ዓ.ም በጀት አመት የአንድኛ (1ኛ) ዙር ጨረታ የተለያዩ እቃዎች እና ሥራዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል – test3.diretenders.com

የአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2019 ዓ.ም በጀት አመት የአንድኛ (1ኛ) ዙር ጨረታ የተለያዩ እቃዎች እና ሥራዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen (Sep 15, 2026)

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

የአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2019 ዓ.ም በጀት አመት የአንድኛ (1ኛ)ዙር ጨረታ፡

  • በሎት1፡- የፅዳት ዕቃዎች ግዥ
  • በሎት 2፡- የደንብ ልብስ በሎት ግዥ
  •  በሎት1፡- አላቂ የቢሮ ዕቃዎች ግዥ
  • በሎት 4፡- የደንብ ልብስ በሎት 4 ግዥ
  • በሎት 5፡- የመኪና እቃዎች ግዥ
  • በሎት 6፡- የኤሌክትሮኒክስ (የአይቲ) እቃዎች ግዥ

ሎት 6 በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

በተጨማሪም በአገልግሎት ሥራዎች ፦

  •  በሎት 1፦- የመስተንግዶ ስራዎች፣
  • በሎት 2፡- የህትመት ስራዎች
  • በሎት 3፦ የኤሌክትሮኒክስ (የአይቲ) እቃዎች ጥገና ስራዎች
  •  በሎት 4፡- የኤሌክትሮኒክስ (የአይቲ) እቃዎች መለዋወጫ አቅርቦት
  •  በሎት 5 የልብስ ስፌት ስራዎች
  •  በሎት 6፡- የቢሮ ቋሚ ዕቃዎች ጥገና ስራዎች
  • በሎት 7 የዲኮር ስራዎችን
  •  በሎት 8፡- የትራንስፖርት አገልግሎት ስራዎች አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።

ስለሆነም ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ሎቶች መስፈርቱን የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች መጫረት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

  1. ተጫራቾች በአቅራቢ ዝርዝር የተመዘገቡ መሆኑን እና የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
  2. የታደሰ የንግድ ፈቃድና የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
  4. ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ቫትን ያካተተ መሆን አለበት።
  5. የጨረታ ሰነዱ የመወዳደሪያ ዋጋ በሙሉ ታሽጎ ለጨረታ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማሰገባት ይኖርባቸዋል።
  6. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ሎት ሁሉ ናሙና ማቅረብ አለባቸው::
  7. ተጫራቾች በአንድ እቃ አይነት ሁለት ናሙና ማቅረብ የለባቸውም::
  8. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ሎት ሁሉ ናሙና ላይ ድርጅታቸውን የሚገልፅ ማንኛዉም ምልክት (ማህተም) ማስቀመጥ የለባቸዉም::
  9. ተጫራቾች የጨረታው ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር በየሎቱ 300 /መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል ከወረዳ 5 ፋይናንስ ጽ/ቤት የጨረታ ሰነዱን መግዛት የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
  10. ጨረታው ከወጣበት ቀን አንስቶ በ11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት የሚታሸግ ሲሆን 4፡30 ሳጥኑ የሚከፈት ይሆናል፡፡
  11. የመወዳደሪያ ዋጋ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ወስጥ ማስገባት የምትችሉ ሲሆን ጨረታው የሚከፈተው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይሆናል።
  12.  ተጫራቾች ዋጋቸውን በወሰዱት የጨረታ ሰድ ይ ብቻ መሙላት ይጠበቅባቸዋል።
  13. ተጫራቾች በወሰዱት ሰነድ ላይ በእስኪርብቶ እስፔክ ማስተካከል አይችሉም።
  14. የጨረታ ዋስትና በየሎቱ 2% ሲፒኦ ብቻ ሲሆን የምንቀበለው ቼክ አንቀበልም በተጨማሪ ተጫራቾች አሸናፊ ሆነው ሲቀርብ አሸናፊ የሆነበትን 10% ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
  15. ተጫራቾች የዋጋ የጊዜ ገደብ ማስቀመጥ አይችሉም::
  16. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ማሳሰቢያ፦ ተጫራቾች ለሚኖራቸው ጥያቄ ወይም መረጃ ለማግኘት ቢፈልጉ በስልክ ቁጥር 01111266384 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ።

አድራሻ ፡- ፒያሳ ገዳም ሰፈር ከጊዮርጊስ ጀርባ ወደ ዳክስን መሄጃ ወረዳ 5 ፋይናንስ ጽ/ቤት 2ኛ ፎቅ::

ራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት