Your cart is currently empty!
በን/ስ/ላ/ክ/ከ/ፖሊስ መምሪያ በስሩ ለሚገኙ ሁሉም ፖሊስ ጣቢያዎች በ2018 ዓ/ም በጀት አመት የሚያስፈልጋቸውን የተለያዩ እቃዎችን አወዳድሮ ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል
Addis Zemen(Oct 16, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
በን/ስ/ላ/ክ/ከ/ፖሊስ መምሪያ እና በስሩ ለሚገኙ ሁሉም ፖሊስ ጣቢያዎች በ2018 ዓ/ም በጀት አመት የሚያስፈልጋቸውን
- ሎት1.የፅህፈት መሳሪያ
- ሎት 2. የፅዳት እቃዎች
- ሎት 3. ህንፃ መሳሪያ
- ሎት 4. የህትመት ውጤቶች
- ሎት 5.መድሃኒት
- ሎት 6. የካምፕ እቃዎች
- ሎት 7. የመኪና ጎማ
- ሎት 8 ደንብ ልብስ
- ሎት 9 የቆሻሻ ፍሳሽ ማስወገጃ መኪና ኪራይ
- ሎት 10. የአካልና የንብረት መፈተሻ ቤት (ቢሮ)
ብቃት ያላቸውንና በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሰረት፡–
- በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው ሆነው በስራ መስኩ የተሰማሩ፤የዘመኑን ግብር የከፈሉ በመንግስት ግ/ን/አስ/ ኤጀንሲ ድህረ ገጽ ላይ በአቅራቢዎች ምዝገባ ዝርዝር የተመዘገቡ፣ የቲን፣ 1የቫት እና TOT ተመዝጋቢ የሆኑና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች የጨረታው ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ለሎት 5 እና 8 ለእያንዳንዱ 3,000.00/ሶስት ሺህ ብር/ ለሎት 1፣2፣7 ለእያንዳንዱ 4,000 /አራት ሺህ ብር / ለሎት 3፣6፣9 ለእያንዳንዱ 5,000/አምስት ሺህ ብር / ለሎት 4 ለአንዱ 6,000.00 (ስድስት ሺህ ብር) ለሎት 10 ለአንዱ 7,000.00 (ሰባት ሺህ ብር) ሲፒኦ /CPO/በመ/ቤታችን ስም (ን/ስ/ላ/ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ) ተዘጋጅቶ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ዕለት አንስቶ በተከታታይ 10 የስራ ቀናት ለአንድ ሎት የማይመለስ 200.00/ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል በን/ስ/ላ/ክ/ከ/ፖሊስ መምሪያ ጀሞ ሚካኤል አደባባይ የግዥ ቢሮ ቁጥር 503 በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያው ከወጣበት እለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት በን/ስ/ላ/ክ/ከ/ፖሊስ መምሪያ ጀሞ ሚካኤል አደባባይ የሚገኝ የግዥ ቢሮ ቁጥር 503 ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል ፡፡ በተጨማሪም ከአንድ ሎት በላይ ሲወዳደሩ በእያንዳንዱ ሎት ከላይ በተ.ቁ 1 ላይ የተጠቀሱትን ሰነዶች አሟልቶና አያይዞ በየሎቱ በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስገባት ይኖርበታል፡፡
- ጨረታው በአስረኛው ቀን ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ታሽጎ በማግስቱ ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት በክ/ከተማው የስብሰባ አዳራሽ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ የመክፈቻ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት ለተወዳደሩባቸው ለሎት ናሙና ማቅረብ የሚኖርባቸው ሲሆን መ/ቤቱ መመዘኛ መስፈርት /Specification/ ባወጣንባቸው ዕቃዎች ላይ ሌላ የራስን መመዘኛ /Specification/ አውጥቶ መወዳደር አይቻልም ::
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን እቃዎች ለእያንዳንዱ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የዘገየ ጨረታና በጨረታ መክፈቻ ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም፡፡
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈፃሚው መ/ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ ለውል ማስከበሪያ 10% ዋስትና መስጠት ይኖርበታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ
አድራሻ ን/ስ/ላ/ክ/ከ/ፖሊስ መምሪያ ጀሞ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አጠገብ
በስልክ ቁጥር 0114423315/0114403319 / 0118334107/ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ
cttx Advertising and Promotion cttx, cttx Building and Finishing Materials cttx, cttx Building Construction cttx, cttx Cleaning and Janitorial Equipment and Service cttx, cttx Construction and Water Works cttx, cttx Construction Machinery and Equipment cttx, cttx Disposal of Hazardous Waste cttx, cttx Equipment cttx, cttx Freight Transport cttx, cttx Hand Tools and Workshop Equipment cttx, cttx Health Care, cttx Metal and Metal Working cttx, cttx Office Supplies and Services cttx, cttx Others cttx, cttx Pharmaceutical Products cttx, cttx Plastic Products cttx, cttx Plastic Raw Materials and Products cttx, cttx Printed Advertising Materials cttx, cttx Printing and Publishing cttx, cttx Promotional Items cttx, cttx Rent cttx, cttx Safety and Security cttx, cttx Shoes and Other Leather Products cttx, cttx Spare Parts and Car Decoration Materials cttx, cttx Stationery cttx, cttx Tents and Camping Equipment cttx, cttx Textile, cttx Transportation Service cttx, cttx Vehicle cttx, cttx Warehousing, Garment and Leather cttx, Garments and Uniforms cttx, Medical Industry cttx, Transit and Transport Service cttx