ቶታል ኢነርጂስ ማርኬቲንግ ኢትዮጵያ አ.ማ. ያገለገሉ ታንከሮችን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል – test3.diretenders.com

ቶታል ኢነርጂስ ማርኬቲንግ ኢትዮጵያ አ.ማ. ያገለገሉ ታንከሮችን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል


Reporter (May 10, 2026)

 ያገለገሉ ታንከሮችን ለመሸጥ የወጣ ጨረታ

TENDER REF: T-189/26/GS/PUR

ቶታልኢነርጂስ ማርኬቲንግ ኢትዮጵያ ኢሚ ያገለገሉ ታንከሮችን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል:: በጨረታው መካፈል የሚፈልግ ከዚህ ቀጥሎ

የተዘረዘሩትን ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት መጫረት ይችላል።

1. ተጫራቾች የዕቃዎቹን ዝርዝር የያዘውን የጨረታ ሰነድ ሙለጌ ህንፃ ሰባተኛ ፎቅ በሚገኘው ቶታልኢነርጂስ ማርኬቲንግ ኢትዮጵያ አ.ማ. ዋናው መ/ቤት በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ::

2. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ከቫት በፊት ከተጠቀሰው ዋጋ ላይ 5% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ወይም CPO. ከጨረታው ሰነድ ጋር ማስገባት አለባቸው::

3. በጨረታ ሰነዱና በC.P.O ላይ የሚጠቀሰው የተጫራች ስም አንድ ዓይነት መሆን አለበት::

4. ታንከሮቹ የሚሸጡት ባሉበት ሁኔታ ነው::

5. ተጫራቾቸ የጨረታውን ሰነድ በፖስታ አሽገው ፖስታው ላይ የተጫራቹን ስም፤ ስልክ ቁጥርና የሚወዳደሩበትን የጨረታ አይነት በፖስታው ላይ በመፃፍ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ማስገባት ይጠበቅባቸዋል::

6. ጨረታው ግንቦት 2 ቀን 2018 ተከፍቶ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ ይዘጋል፡

7. ቶታልኢነርጂስ ማርኬቲንግ ኢትዮጵያ አ.ማ. የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

ቶታል ኢነርጂስ ማርኬቲንግ ኢትዮጵያ አ.ማ.

ዋናው መስሪያ ቤት የግዥ ክፍል

ሳሪስ መንገድ ቡና ቦርድ ፤ ሙለጌ ህንፃ 7ኛ ፎቅ

ስልክ፣ 011 465 3044 ወይም 011 466 8025


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *