Addis Zemen (Jun 06, 2026)
የጣውላ ምርት ግልጽ ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር OFWE/XA08/2018
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት በእያንዳንዱ የጣውላ ዓይነት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ
1. በአርሲ ቅ/ጽ/ቤት በተለያዩ የእንጨት መሰንጠቂያ ላይ የተዘጋጀ ጣውላ፣
2 በጅማ ቅ/ጽ/ቤት በተለያዩ የእንጨት መሰንጠቂያ ላይ የተዘጋጀ ጣውላ፣
3. በባሌ ቅ/ጽ/ቤት በተለያዩ የእንጨት መሰንጠቂያ ላይ የተዘጋጀ ጣውላ፣
4. በቦረና ጉጂ ቅ/ጽ/ቤት በተለያዩ የእንጨት መሰንጠቂያዎች ላይ የተዘጋጀ ጣውላ፣
5. በፊንፊኔ ቅ/ጽ/ቤት በተለያዩ የእንጨት መሰንጠቂያ ላይ ተከፋፍሎ የተዘጋጀ ጣውላ፣
6. በሐረርጌ ቅ/ጽ/ቤት በተለያዩ የእንጨት መሰንጠቂያ ላይ ተከፋፍሎ የተዘጋጀ ጣውላ፣
7. በኢሉአባቦራ ቅ/ጽ/ቤት በተለያዩ የእንጨት መሰንጠቂያ ላይ የተዘጋጀ ጣውላ፣
8. በወለጋ ቅ/ጽ/ቤት የእንጨት በተለያዩ የእንጨት መሰንጠቂያ ላይ የተዘጋጀ ጣውላ፣
በመሆኑም፡–
- የጣውላ የቤትና የቢሮ እቃዎችና ተዛማጅ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው ድርጅቶች እና ግለሰቦች እንዲሁም Tin number ያላቸውና እና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ ስለ ጨረታው ዝርዝር ሁኔታ የሚገልጽ የጨረታ ሰነድ ለእያንዳንዳቸው200/ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ቀበና ሼል /ኦይል ሊቢያ አጠገብ በሚገኘው የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ዋና መ/ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201 እና ጨረታው በሚወጣበት በጂማ ቅ/ጽ/ቤት (ጂማ)በኢሉአባቦራ ቅ/ጽ/ቤት (መቱ) በአርሲ ቅ/ጽ/ቤት (አርሲ ነጌሌ)ፊንፊኔ ቅ/ጽ/ቤት (ፊንፊኔ) በሐረርጌ ቅ/ጽ/ቤት (ጭሮ) በቦረና ጉጂ ቅ/ጽ/ቤት (አዶላ) በባሌ ቅ/ጽ/ቤት (ጎባ) በወለጋ ቅ/ጽ/ቤት (ግምቢ) በመግዛት በጨረታዉ መሣተፍ ይችላሉ።
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታተይ ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል።
- ጨረታው የሚዘጋበት እና የሚከፈትበት ቀንና ሰዓት በጨረታው ሰነድ ውስጥ ይገለጻል።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid bond) የሚሆን ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 5% በማስላት በድርጅቱ ዋና መ/ቤት የምትጫረቱ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ከሚገኙ ባንኮች በቅ/ጽ/ቤት የምትጫረቱ መ/ቤቱ ከሚገኝበት ከተማ በባንክ በተረጋገጠ ደረሰኝ (cpo) ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
- ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ለተጨማሪ መረጃ www.oromiaforest.et , በስልክ ቁጥር 011 124 0249 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት