በአ/ከ/ክ/ከተማ የወረዳ 5 ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት ለተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል – test3.diretenders.com

በአ/ከ/ክ/ከተማ የወረዳ 5 ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት ለተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል


Addis Zemen (Aug 28, 2026)

1ኛ ዙር ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር፣ አ/ከ/ክ/ከ/ወ/5/ፋ/ጽ/001/19

በአ/ከ/ክ/ ከተማ የወረዳ 5 ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት ለተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል።

ሎት ቁጥር

የሎት ዝርዝር

ከጠቅላል ዋጋ የሚያሲዙት/የብር መጠን/

ሎት 1

የደንብ ልብስ

27,234.85

ሎት 2

ቋሚ ዕቃዎች

5,000.00

ሎት 3

የቢሮ የጽህፈት መሳሪያዎች

15,448.42

ሎት 4

የፅዳት ዕቃዎች

18,469.14

ሎት 5

የቢሮ መስተንግዶ

22,648.8

ሎት 6

የመኪና ኪራይ

14,593.59

ሎት 7

የተለያዩ የዲኮር ስራዎች

5,003.75

ሎት 8

የጉልበት ሰራተኛ

5,250.00

ሎት 9

የሕትመት ስራዎች

1000.00

ሎት 10

የደንብ ልብስ ስፌት

10,000.00

ሎት 11

የተለያዩ የግብርና ዘሮች

4,500.00

ሎት 12

የሰራተኞች መዝናኛ ክበብ

22,648.8

በመሆኑም ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶችን የምታሟሉ ተጫራቾች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል።

  • የዘመኑን ግብር ከፍለው የታደሰ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉና የግብር መለያ ቁጥር ያላቸው።
  • የቫት/TIN NO/ ተመዝጋቢ የሆኑና በአቅራቢዎች ዝርዝር በዌብ ላይት ስለመመዝገባቸው መረጃ የምናይ መሆኑን
  • ተጫራቾች ለመወዳደር የጨረታ ሰነድ ስታስገቡ ለተወዳደራችሁበት አላቂ ዕቃ እና የልብስ ስፌት ሳምፕል ማቅረብ ይኖርባችኋል።
  • ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ /cpo/ ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ 0.5% በማስላት በማስያዝ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ይህን ካላቀረቡ ከውድድር ውጪ ይሆናሉ።
  • ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት በማይመለስ ብር በካሽ 200.00 /ሁለት መቶ/ ብር በመክፈል በወረዳ 5 ፋ/ጽ/ቤት 2ተኛ ፎቅ ወደ ቢሮው ሲገቡ በስተቀኝ በመግባት መግዛት ይችላሉ።
  • የጨረታ ሠነዱ በተጫራቾች መሞላት ያለባቸው ከፍሎች በሙሉ መሞላት አለባቸው።
  • በስራ ኢንተርፕራይዝ የተደረጃችሁ በራሳችሁ ምርት ላይ ልዩ አስተያየት ስለሚደረግ አምራች መሆናችሁን የሚገልፅ መረጃ ካደራጃችሁ አካል የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ አለባችሁ።
  • በስራ ኢንተር ፕራይዝ የተደራጃችሁ ከምታመርቱት ምርት ውጪ ባለ ዘርፍ እና ሰነድ ላይ እንደማንኛውም ተጫራች ድርጅት cpo ማስያዝ ይኖርባችኋል።
  • ለሰራተኞች ካፍቴርያ መብራት ክፍያ በወር 4,000 ውሃ የቤት ኪራይ ‘የመስሪያ ቁሳቁሶች ከመ/ቤቱ የሚቀርብ ይሆናል።
  • ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ ሲያቀርቡ ቫትን አካተው ዋናውንና ኮፒውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
  • ጨረታው በ11ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 4፡30 ይከፈታል።
  • ጨረታው ከተዘጋ በኋላ የሚቀርብ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
  • ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታ ራሱን ማግለል አይቻልም።
  • የተጫራቾችን አድራሻ የሚገልፅ ሙሉ መረጃ ከሰነዱ ጋር መያያዝ አለበት።
  • መስሪያ ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  • ተጫራቾች የውል ማስከበሪያ ካሽነፈው ዕቃ ከጠቅላላ ዋጋ 10% በባንከ የተረጋገጠ /cpo/ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • ተጫራቾች የቢሮ መስተንግዶ ላይ የምትወዳደሩ የውሃና የቆሎ ሳምፕል ማቅረብ አለባችሁ። ሳምፕል ያላቀረበ ተጫራች ድርጅት ከጨረታ ውጭ ይሆናል።
  • አሸናፊ ተጫራች ድርጅት የአሸነፋችሁትን ዕቃ በራሳችሁ ትራንስፖርት በማጓጓዝ ማቅረብ አለባችሁ።

አድራሻ፡- ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጳውሎስ ቅርንጫፍ ወደ አበበ ቢቂላ ስታዲየም መውረጃ 300 ሜትር ገባ ብሎ ይገኛል፡።

ለበለጠ መረጃ፦ ስልክ ቁጥር 011-230-6998 / 09 27 60 26 30/

ማሳሰቢያ፡-

  • በተጫረታችሁበት ዕቃ ላይ ዋጋ ስታስገቡ ቫትን ያካተተ መሆን ይጠበቅብዎታል መወዳደር የሚቻለው ንግድ ፍቃዱ ላይ በተሰጠው ስራ ዘርፍ ብቻ ነው።
  • ተጫራቾች ያስገባችሁትን ሳምፕል በቂ ማስቀመጫ ቦታ ስለሌለን አሸናፊና ተሸናፊ ከተለየ በኋላ በ60 ስልሳ የስራ ቀናት ውስጥ እንድትወስዱ እያሳሰብን በተቀመጠው ቀናቶች ውስጥ የማይወስድ ተጫራች ጽ/ቤቱ መስሪያ ቤቱ ሃላፊነቱን አይወስድም።
  • ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዛችሁትን cpo ለውል ማስከበሪያ ማዞር ማስያዝ አይቻልም።
  • ተጫራቾች ዋና የጨረታ ሰነድ ላይ ክፍል 2/ሁለት/ እና ክፍል 6/ስድስት/ በተጫራቾች የሚሞላውን ቅጽ መሙላት እና በየአንድአንዱ ገጽ ላይ ፊርማና የድርጅታችሁን ማህተም በማድረግ የጨረታ ሰነዱን መመለስ ይኖርባችኋል። ነገር ግን ከፍል 2 እና ክፍል 6 ላይ በተጫራቾች የሚሞላውን ቅፅ ያልሞላ ተጫራች እና
  • የጨረታ ሰነዱን ካልመለሰ /ተመላሽ ካላደረገ ከላይ የተጠቀሱትን ያላሟላ ተጫራች ጨረታው ውድቅ ይሆንበታል።
  • ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያም ሆነ ለውል ማስከበሪያ የምታሲዙት በCPO ብቻ ነው። ከሲፒኦ ውጪ በቼክና በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አይቻልም። ካስያዛችሁም ከውድድር ውጪ ትሆናላችሁ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት