በምዕራብ ጎጃም ዞን በሰከላ ወረዳ የአባይ ምንጭ 2ኛ ደ/ት/ቤት ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል የተማሪዎች መማሪያ እና ማስተማሪያ መጽሐፍቶች በትምህረት ካሪኩለም መቀየር ምክንያት ከጥቅም ውጭ የሆነ በመሆኑ በኪሎ በግልጽ ጨረታ የአንድ ኪሎ መነሻ ዋጋ ብር 5.50 (አምስት ብር ከአምሳ ሳንቲም) ሆኖ በዘርፉ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸውን ተወዳዳሪዎች አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል – test3.diretenders.com

በምዕራብ ጎጃም ዞን በሰከላ ወረዳ የአባይ ምንጭ 2ኛ ደ/ት/ቤት ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል የተማሪዎች መማሪያ እና ማስተማሪያ መጽሐፍቶች በትምህረት ካሪኩለም መቀየር ምክንያት ከጥቅም ውጭ የሆነ በመሆኑ በኪሎ በግልጽ ጨረታ የአንድ ኪሎ መነሻ ዋጋ ብር 5.50 (አምስት ብር ከአምሳ ሳንቲም) ሆኖ በዘርፉ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸውን ተወዳዳሪዎች አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል


Be'kur (Sep 07, 2026)

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

በምዕራብ ጎጃም ዞን በሰከላ ወረዳ የአባይ ምንጭ 2ኛ ደ/ት/ቤት ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል የተማሪዎች መማሪያ እና ማስተማሪያ መጽሐፍቶች በትምህረት ካሪኩለም መቀየር ምክንያት ከጥቅም ውጭ የሆነ በመሆኑ በኪሎ በግልጽ ጨረታ የአንድ ኪሎ መነሻ ዋጋ ብር 5.50 (አምስት ብር ከአምሳ ሳንቲም) ሆኖ በዘርፉ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸውን ተወዳዳሪዎች አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

ስለዚህ፡-

  1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው።
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው።
  3. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
  4. የሽያጩ ብር መጠን ከብር 200,000 (ከሁለት መቶ ሺህ ብር) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
  5. በጨረታው የሚሳተፉት ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም 11/2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡30 ድረስ የጨረታ ሰነዱን አባይ ምንጭ 2ኛ ደ/ት/ቤት ቢሮ ቁጥር 06 ዘወትር በስራ ሰዓት በመምጣት መግዛት ይችላሉ።
  6. ተጫራቾች ብር 10,000 (አስር ሺህ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ሲፒኦ) በጥሬ ገንዘብ፣ በኢትዮጲያ ብሄራዊ ባንክ በተፈቀደላቸው የታወቁ ባንኮች ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ደረሰኝ ለአባይ ምንጭ 2ኛ ደ/ት/ቤት ብለው ማቅረብ አለባቸው።
  7. የሚሸጠውን የተማሪዎች መማሪያ እና ማስተማሪያ መጽሐፍቶች አይነት እና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ስነዱ ማግኘት ይችላሉ። ለሽያጭ የሚስፈልገውን ሚዛን አሸናፊው አባይ ምንጭ 2ኛ/ደ/ት ቤት ድረስ ማምጣት ይኖርበታል።
  8. አሽናፊው የሚለየው የአንዱ ኪሎ ዋጋ ከፍተኛ የሞላ ይሆናል።
  9. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዱን ይህ የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የሻጩን መስሪያ ቤት ስምና አድራሻ በማህተም እና ፊርማ አስደግፎ የሻጩ መስሪያ ቤት አባይ ምንጭ 2ኛ ደ/ት/ቤት ባዘጋጀው የጨረታ ማስገቢያ ሳጥን ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ መስከረም 12/2019 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል። በዚያው ቀን 4፡10 የጨረታ ማስገቢያ ሳጥኑ ይታሸጋል።
  10. ጨረታው የሚከፈተው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት በኋላ በ16ኛው ቀን የጨረታ ማስገቢያ ሳጥኑ በታሸገበት በዚያው እለት ከረፋዱ 4፡15 መገኘት በፈለጉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት በአባይ ምንጭ 2ኛ ደ/ት/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ይከፈታል። ተጫራቾች ባይገኙም ጨረታውን ለመክፈት አያስተጓጉለውም።
  11. የመክፈቻ ቀኑ የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
  12. አሸናፊው ከተለየበት ቀን ጀምሮ ከ5 የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የመጽሐፍቶች መለኪያ ሚዛን ይዘው በማምጣት ከት/ቤቱ ጋር ውል በመያዝ ውል ከያዙበት ቀን ጀምሮ እስክ 20 ተከታታይ ቀናት ድረስ የገዙትን የተማሪዎች መማሪያ እና ማስተማሪያ መጽሐፍቶች ማንሳት ይጠበቅበታል።
  13. ት/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  14. ለበለጠ መረጃ ለማግኘት እና የሚሸጠውን የተማሪዎች መማሪያ እና ማስተማሪያ መጽሐፍት ያለበትን ሁኔታ ለማወቅ ከፈለጉ አባይ ምንጭ 2ኛ ደ/ት ቤት ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት በአካል በመምጣት ማግኘት ይችላሉ።

ማሳሰቢያ፡- ከተጠቀሰው ዝርዝር (ስፔስፊኬሽን) ውጭ የራሱን (ስፔስፊኬሽን) የሞላ ተጫራች ከጨረታ ውድድር ውጭ ሆኖ በተጨማሪም ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን እንገልጻለን።

የአባይ ምንጭ 2ኛ ደ/ት/ቤት


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *