Your cart is currently empty!
ኒያላ ኢንሹራንስ አ.ማ. ጉዳት ደርሶባቸው ለደንበኞች ተገቢውን ካሣ ከከፈለ በኋላ የተረከባቸውን ቀረጥ የተከፈለባቸውና ያልተከፈለባቸው ተሽከርካሪዎችን እንዲሁም፤ መለዋወጫዎች እና ያገለገሉ የቢሮ ዕቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል
Reporter(Oct 26, 2025)
ከስር የተቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ። Please read the detailed instructions below.
የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር SD/55/25
ኒያላ ኢንሹራንስ አ.ማ. ጉዳት ደርሶባቸው ለደንበኞች ተገቢውን ካሣ ከከፈለ በኋላ የተረከባቸውን ቀረጥ የተከፈለባቸውና ያልተከፈለባቸው ተሽከርካሪዎችን እንዲሁም፤ መለዋወጫዎች እና ያገለገሉ የቢሮ ዕቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ተጫራቾች በኩባንያው የተዘጋጀውን የጨረታ ዝርዝር መመሪያና ዋጋ ማቅረቢያ ሠነድ ከኩባንያው የተጎዱ ተሽከርካሪዎች ማከማቻ–ቃሊቲ/Wreck Yard/ የማይመለስ ብር 50.00 /ሃምሳ ብር/ ከፍለው በመውሰድ ይህ ማስታዎቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ የሚዎዳደሩባቸውን ንብረቶች ዝርዝር በመግለጽ እስከ ህዳር 1 ቀን 2018 ዓ/ም ጧት 4፡00 ሰዓት ድረስ በሰም በታሸገ ፖስታ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 04 ሚኪሊላንድ መንገድ በሚገኘው ፕሮቴክሽን ሀውስ በምድር ቤት ዋናው መግቢያ ላይ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ የሚገዙትን ዕቃ ዋጋ ከነቫቱ በመግለጽ በኩባንያው መነሻ ዋጋ ላይ 10% የጨረታ ዋስትና ለኩባንያው በባንክ በተረጋገጠ ቼክ (CPO) አሠርተው ከጨረታው ሠነድ ጋር ገቢ ማድረግ ይኖርባቸዋል።
ጨረታው በዕለቱ ኅዳር 1 ቀን 2018 ዓ/ም ከጧቱ 4፡30 ሰዓት በኩባንያው የሠራተኞች ክበብ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጫራታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ኒያላ ኢንሹራንስ አ.ማ.
የስልክ ቁጥር 011-6-626667