Addis Zemen (Apr 13, 2026)
በጉምሩክ ኮሚሽን የድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት የጨረታ ማስታወቂያ
የግልጽ ጨረታ ቁጥር O4/2018
በጉምሩከ ኮሚሽን የድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት ውርስ ሆኖ በመጋዘን የሚገኝ ባለ ሶስት እግር ተሸከርካሪዎች ይህ ማሰታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በግልጽ ጨረታ ባለበት ሁኔታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት፡–
በግልጽ ጨረታ ቁጥር 04/2018 በ13/04/2018 ዓ.ም ባለበት ሁኔታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡
ስለዚህ ለጨረታ የቀረቡት ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎችን በመጫረት የሚፈልግ ተጫራች፡–
- ማንኛውም ዕድሜው ከ18ዓመት በላይ የሆነ ኢትዮጵያዊ ዲጂታል የብሔራዊ መታወቂያ ያለው
- ለጨረታ የቀረበ ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪ ሲሆን የሚገኘው ሙዲአነኖ ግቢ በሚገኘው ተሽከርካሪ መጋዘን ውስጥ ነው።
- የተሸከርካሪው አስመጪ ወይም ባለቤትና ቤተሰብ የሆነ ሰው በጨረታ መሳተፍ አይችልም።
- በጨረታው ሰነድ ላይ በተገለጸው መስፈርት ለመሳተፍ የሚፈልግ ማንኛው ተጫራች የጨረታ ሰነዱን ድሬዳዋ ጉምሩክ ኮሚሽን ገቢ አሰባሰብ እና ዋስትና አያያዝ ቡድን ገንዘብ ያዥ ቢሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከረቡዕ 5/8/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አርብ ከጠዋቱ 1፡30 ሰዓት ሰዓት እስከ ቀኑ 12፡00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ከ2፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት ድረስ በመቅረብ ብር 100 በመክፈል ሰነዱን በመግዛት ተሽከርካሪው በሚገኝበት መጋዘን በመቅረብ ማየት ይቻላል።
- ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪውን ሳያዩ ዋጋ ሰጥቶ ለሚፈጠረው ችግር የቅ/ጽ/ቤቱ ተጠያቂ አይሆንም።
- ጨረታው የሚካሄድበት ቦታ ድሬዳዋ ሙዲአነኖ የሚገኘው ግቢ ውስጥ ነው።
- ተጫራቾች ባለ ሶስት እግር ለተሽከርካሪው የሚሰጡት ዋጋ ከቫት በፊት ያለውን ዋጋ መሆን አለበት።
- ተጫራቾች ተሽከርካሪውን ለመግዛት ለጨታው ዋሰትና ማስከበሪያ 5% በንግድ ባንክ የተረጋገጠ (CPO) በድሬዳዋ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ስም ማሠራት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች በግልጽ ጨረታ የሞሉትን የጨረታ ሰነድ እና ከላይ የተጠቀሱትን መረጃዎች በማያያዝ በዕለቱ በፖስታ ውስጥ በማሸግ ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ 3፡45 ሰዓት ድረስ በድሬዳዋ ሙድአነኖ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
- ጨረታው ከጠዋቱ 3፡50 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድሬዳዋ ሙድአነኖ ጉምሩክ ለጨረታ በተዘጋጀው ቦታ ሣጥኑ ይከፈታል።
- በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ያስያዘው ሲፒኦ ከሚከፍለው ዋጋ ጋር የሚታሰብ ሲሆን ተሸናፊ ተጫራቾች ደግሞ ሲፒኦ በሶስት የሥራ ቀናቶች ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
- የጨረታ አሸናፊ የሆነ ተጫራች የተወዳደሩበትን ተሸከርካሪ አሸናፊ ስለመሆኑ በደብዳቤ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የሥራ ቀናቶች ውስጥ የአሸነፈበት ገንዘብ ገቢ በማድረግ ተሽከርካሪውን መረከብ ይኖርበታል።
- ከላይ በተራ ቁጥር 12 ላይ በተገለጹት ቀናቶች ውስጥ ከፍያውን ፈጽሞ ተሽከርካሪውን ያልተረከበ ተጫራች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘውን ሲፒኦ ለባለሥልጣኑ መ/ቤት ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሚ ለጨረታ ይቀርባል።
- የጉምሩከ ኮሚሽን የድ/ዳ/ቅ/ጽ/ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር፡– 09 15 46 09 70/ 09 12 88 57 46 መደወል ይቻላል።
በጉምሩክ ኮሚሽን የድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት