Reporter (Apr 22, 2026)
በድጋሚ የወጣ ያገለገለ ተሽከርካሪ እና ጄኔሬተር
ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የጉምሩክ ቀረጥ የተከፈለበት 1 /አንድ/ ያገለገለ ተሽከርካሪ ለ3ኛ ጊዜ እና 1 (አንድ) ያገለገለ ጄኔሬተር ለሁለተኛ ጊዜ ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል::
ስለዚህ ማንኛውም ተጫራች፡–
- የተሽከርካሪውን እና የጄኔሬተሩን ሁኔታ በድርጅቱ በመገኘት ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ ጨረታ ሰዓት ድረስ ማየት ይቻላል::
- የጨረታ ማስከበሪያ/ ቢድ ቦንድ/ የተሽከርካሪ እና የጄኔሬተር ከተ.እ.ታ በፊት የሚገዛበትን ዋጋ 10% ከጨረታው መዝጊያ ሰዓት በፊት በጥሬ ገንዘብ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ገቢ ማድረግ ወይም በሲፒኦ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ ይኖርበታል::
- የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 1,000.00 /አንድ ሺህ ብር/ በመክፈል ከድርጅቱ ማርኬቲንግ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 2 በመቅረብ መግዛት ይቻላል::
- የዋጋ ማቅረቢያና ሌሎች መረጃዎች የያዘውን የጨረታ ሰነድ በታሽገ ኢንቨሎኘ ከጨረታ መዝጊያ ሰዓት በፊት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለበት::
- ጨረታው ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ላገለገለ መኪና ከጠዋቱ 4፡15 ተዘግቶ በዚሁ ዕለት 4፡30 እና ላገለገለ ጄኔሬተር ከጠዋቱ 4፡45 ተዘግቶ በዚሁ ዕለት 5፡00 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ ውስጥ ይከፈታል::
ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 01114 163 978 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት