Reporter (May 13, 2026)
የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን
ብረታ ብረቶች ህጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ ላላቸው ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ኮርፖሬሽናችን ሳሪስ በሚገኘው ግቢ ውስጥ ያሉትን ያገለገሉ ብረታ ብረቶች፣ንቃይ ቆርቆሮች እና ቁርጥራጭ የተሸከርካሪና ሌሎች በመሆኑም በጨረታ ላይ መወዳደር የሚፈልጉ ድርጅቶች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መመዘኛዎች ማሟላት አለባቸው።
1. ስለአሻሻጡ የተዘጋጀውንና የጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 1000 /ብር አንድ ሺህ/ በመክፈል ከግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ ከግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም. ዘወትር ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው ከዋናው መ/ቤት /አዲስ አበባ/ ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 3፡00-6፡30 እንዲሁም ከሠዓት ከ7፡30-11፡30 እና ቅዳሜ ከ3፡00 እስከ 6፡30 ሠዓት መግዛት ይችላሉ።
2. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን እስከ ጨረታው መዝጊያ ዕለት እስከ ከግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጧቱ 4፡30 ሠዓት ድረስ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
3. ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ንብረት 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ ብር/ የጨረታ ማስከበሪያ በሲ.ፒ.ኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ስም አሰርተው ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ አለባቸው።
4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ ሲሞሉ በግልጽ 15% የተጨማሪ እሴት ታክስ /AT/ ማሳየት አለባቸው።
5. ጨረታው ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጧቱ 4፡30 ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጧቱ 4፡30 ሠዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዋናው መ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል።
6. የጨረታው አሸናፊ ተጫራች በጨረታው ያሸነፉትን ንብረት ሙሉ ክፍያ በ 5 /አምስት/ የሥራ ቀናት ውስጥ በመክፈል ማንሳት ይኖርባቸዋል በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ ካላነሳ ከ5ኛው ቀን በኋላ ላላነሳበት ቀን በየቀኑ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ ቅጣት የሚከፍል ይሆናል።
7. አሸናፊው በራሱ ወጪ የተለያዩ ብረታ ብረቶች፣ንቃይ ቆርቆሮች እና ቁርጥራጭ የተሸከርካሪና ሌሎች ብረታ ብረቶች ማንሳት፣ ማስጫንና ማጓጓዝ ይኖርበታል።
8. ኮርፖሬሽኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ይሁን በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ። ለማንኛውም ማብራሪያ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 011-416-7347/ 011-466-9336 መጠየቅ ይቻላል።
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን
አድራሻ፡– በቅሎ ቤት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ ፊት ለፊት
ስልክ ቁጥር 011 467-1902/011 416-3483 አዲስ አበባ–ኢትዮጵያ