የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የተለያዩ መጠን ያላቸው ብረታ ብረቶችና ኤሌክሮዶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል – test3.diretenders.com

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የተለያዩ መጠን ያላቸው ብረታ ብረቶችና ኤሌክሮዶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል


2merkato.com (Jun 29, 2026)

የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 1/2019

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የተለያዩ መጠን ያላቸው ብረታ ብረቶችና ኤሌክሮዶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፤

ማንኛውም ተጫራች፡-

  • በዘርፉ ወይም በተመሳሳይ ህጋዊና የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያለው፣ ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገበ መሆኑን እና የታክስ ክፍያ መለያ ቁጥር (TIN) የሚያጋግጥ የምስክር ወረቀት፣ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ ተጫራቾች ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ ስለመሆናቸው በግብር ሰብሳቢው ባለስልጣን የተሰጠ በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የታደሰ ክሊራንስ እንዲሁም በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ መመዝገባቸውን የሚገልፅ ሰነድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣
  • ለእያንዳንዱ የጨረታ ዓይነት የማይመለስ ብር 500/አምስት መቶ ብር/ በመክፈል በስራ ሰዓት ከግዥና ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 3ዐ ዝርዝር መረጃ የያዘውን የጨረታ ሠነድ ማግኘት ይችላል፣
  • የጨረታ ማስከበሪያ/ቢድቦንድ/ ለሚጫረትበት የጠቅላላ ዋጋውን 2% በሲ.ፒ.ኦ፣ በባንክ ጋራንቲ ወይም በጥሬ ገንዘብ በድርጅቱ ደረሰኝ ማስያዝ ይኖርበታል፣
  • የጨረታ ሰነዶችና ከጨረታው ጋር ተያያዥ የሆኑ ሠነዶችን በፖስታ በማሸግ ከጨረታ መዝጊያው ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለበት፣
  • ጨረታው ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡ዐዐ ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡3ዐ ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ ውስጥ ይከፈታል፡፡ በጨረታ አከፋፈት ሂደት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙ የጨረታ ሂደቱን አያስተጓጉለውም፡፡
  • ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር ዐ114 66 – 47 – 05 መጠየቅ ይቻላል፡፡

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *