Addis Zemen (Aug 27, 2026)
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የጅማ ግብርና ምህንድስና ምርምር ማዕከል ለ2019 ዓ.ም የበጀት ዘመን የሚዉል
- የፅዳት እቃ፣
- የጽሕፈት መሣሪያ፣
- የወርክሾፕ
- አላቂ ብረታብረትና
- ሌሎች የምርምር ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል.
ዝርዝር ሁኔታዎች
ተጫራቾች ይህ ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ስለዕቃዎቹ የሚገልጽ ሰነድ ዶክመንት/ የማይመለሰ ብር 400 /አራት መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት ጅማ ግብርና ምህንድስና ምርምር ማዕከል ሕንፃ ቁጥር 3 ቢሮ ቁጥር 2 ድረስ በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
የተጫራቾች ገዴታዎች፡–
- ተጫራቾች ተፈላጊ እቃዎችን ማቅረብ የሚያስችላቸው የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉና ለዚህም ሕጋዊ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
- የቫት/የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢና የምዝገባ የምስክር ወቀረት ማቅረብ አለባቸው።
- የዚህ ጨረታ ተካፋዮች በገንዘብና አኮኖሚ ልማት ሚ/ር በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡና የምስክር ወረቀት ያላቸውና ኦሪጅናልና ኮፒውን ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ 2% በባንክ በተመሰከረ CPO /ሲፒኦ/ የጨረታ ዋስትና ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በጨረታ ሰነድ ላይ በመሙላት በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 /አስራ አምስት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ዘወትር በሥራ ሰዓት ጠዋት 2:30-6:30 ከሰአት ከ7:30-11:30 ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ በግዥ ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር ክፍል ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
- ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3:30 ሰዓት ተጫራቾች በተገኙበት ይከፈታል የመክፈቻው ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ወይም በሕዝባዊ በዓላት ላይ ከዋለ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
- ማዕከሉ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፡–
የስልክ ቁጥሮች 047 111 2424 ወይም በሞባይል 09 17 05 43 61 መደወል ይቻላል።
የጅማ ግብርና ምህንድስና ምርምር ማዕከል
/ጅማ/