በምሥራቅ ደንምቢያ ጤና ጥበቃ ስር የሚገኘው የአይምባ ጤና ጣቢያ የAPTS ሸልፍ ለማሰራት ይፈልጋል – test3.diretenders.com

በምሥራቅ ደንምቢያ ጤና ጥበቃ ስር የሚገኘው የአይምባ ጤና ጣቢያ የAPTS ሸልፍ ለማሰራት ይፈልጋል


Be'kur (Sep 07, 2026)

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

በምሥራቅ ደንምቢያ ጤና ጥበቃ ስር የሚገኘው የአይምባ ጤና ጣቢያ የAPTS ሸልፍ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉት መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በግልጽ ጨረታ መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. ህጋዊ ደረሰኝ ያላቸው፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸው የሚያረጋግጡ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እና ጥሩ ስነምግባር ያላቸው፡፡
  5.  ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን አይምባ ጤና ጣቢያ ግዥ/ፋ/አስ/ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 12/2019 ዓ.ም በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ከረፋዱ 3፡30 ታሽጉ ከረፋዱ 4፡00 ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ሆኖም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሰዓቱ መገኘት ካልቻሉ ጨረታው ሰዓቱን ጠብቆ የሚከፈት ይሆናል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሃሳባቸውን አንድ ወጥ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ከፖስታውና ከእያንዳንዱ ገጽ ላይ የድርጅታችሁ ማህተም በማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ግዥ ጠቅላላ ዋጋ ቫትን ጨምሮ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  8. የጨረታ ሰነድ መግዣ የሚሆን ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) ከካርድ ክፍል መግዛት ይችላሉ፡፡
  9. መ/ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ማግኘት ከፈለጉ አይምባ ጤና ጣቢያ ፋን/አስተ በመምጣት ወይም በስልክ ቁጥር 09 18 08 07 09 ደውለው መረጃ መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የአይምባ ጤና ጣቢያ


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *