በሕግ በመፍረስ ላይ ያለው የብሔራዊ መሐንዲሶችና ሥራ ተቋራጮች ድርጅት ያገለገሉ የቆርቆሮ መጋዘኖችን በራሱ ወጪ በማፍረስ ቆርቆሮዎችን እና ፍራሽ እንጨቶችን እንዲሁም የተለያዩ የቢሮ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታ በጥቅል በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል – test3.diretenders.com

በሕግ በመፍረስ ላይ ያለው የብሔራዊ መሐንዲሶችና ሥራ ተቋራጮች ድርጅት ያገለገሉ የቆርቆሮ መጋዘኖችን በራሱ ወጪ በማፍረስ ቆርቆሮዎችን እና ፍራሽ እንጨቶችን እንዲሁም የተለያዩ የቢሮ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታ በጥቅል በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል


Addis Zemen (Apr 15, 2026)

የቆርቆሮ መጋዘኖችን እና ሌሎች የቢሮ ዕቃዎችን ለመሸጥ በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ

ቁጥር 01/2018

በሕግ በመፍረስ ላይ ያለው የብሔራዊ መሐንዲሶችና ሥራ ተቋራጮች ድርጅት ያገለገሉ የቆርቆሮ መጋዘኖችን በራሱ ወጪ በማፍረስ ቆርቆሮዎችን እና ፍራሽ እንጨቶችን እንዲሁም የተለያዩ የቢሮ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታ በጥቅል በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል።

ስለሆነም፡-

1. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የሥራ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላል፡፡

2. የጨረታ ሰነዱን ከገዙበት ቀን ጀምሮ ኮተቤ በሚገኘው ብሔራዊ መሐንዲሶችና ሥራ ተቋራጮች ድርጅት ግቢ በመገኘት ንብረቶቹን መመልከት ይችላሉ፡፡

3. ተጫራቹ ለመጫረት ከሚያቀርበው ዋጋ 10% የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ /Bid Bond/ በባንክ በተመሠከረለት ቼክ /CPO/ በመ/ቤቱ ትክከለኛ ስም በማሠራት ከጨረታ ሠነዱ ጋር በማያያዝና በፖስታው ላይ የተጫራቹን ስምና አድራሻ በመግለጽ እስከ ጨረታው መዝጊያ ሚያዝያ 29 ቀን 2018ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ድረስ ቢሮ ቁጥር 2 ለዚሁ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡

4. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመ/ቤቱ መሠብሠቢያ አዳራሽ ሚያዝያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡ዐዐ ሰዓት ተዘግቶ 4፡30 ይከፈታል።

5. በቂ የዋስትና ማሰከበሪያ CPO ያላስያዙ ተጫራቾች ኮሚቴው ከጨረታው የመሰረዝ መብት አለው፡፡

6. የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያው ለአሽናፊዎች ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሽናፊዎች የጨረታ ውጤት እንደፀደቀ ይመለስላቸዋል፡፡

7. ተጫራች ያሸነፋቸውን መጋዘኖች በራሱ ወጪ በማፍረስ እና በትራንስፖርት በተሰጠው ጊዜ ገደብ ንብረቱን ማንሳት ይኖርበታል፡፡

8. የጨረታው አሸናፊዎች በውጤቱ መሠረት ክፍያውን ከፈፀሙ በኋላ ያሸነፋባቸውን ንብረቶች በ15 ቀናት ውስጥ መጋዘኖችን በማፍረስ ቆርቆሮዎቹ እና ፍራሽ እንጨቶችን አንስተው ማጠናቀቅ አለባቸው፡፡

9. ከላይ በተጠቀሰው 15 ቀናት ውስጥ ንብረቱን አጠናቆ ያልወሰደ ተጫራች የጥበቃና የቦታኪራይ በቀን ብር 500.00 እንዲከፍል ይደረጋል፡፡

10. መ/ቤቱ ለአሻሻጡ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻ፡- በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 13 ስልክ ቁጥር 0913019601

ከአራራት ሆቴል ወደ ወሰን በሚወሰደው አዲስ አስፋልት ከፍ ብሎ አቤም ሆቴል ፊት ለፊት፡፡

በሕግ በመፍረስ ላይ ያለ የብሔራዊ መሐንዲሶችና ሥራ ተቋራጮች ድርጅት

አዲስ አበባ