በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ ንብረትነቱ የተለያዩ የኦሮሚያ መ/ቤቶች ከአገልግሎት ውጭ የሆኑ በቢሮ፤ ዞን፤ ከተማና ወረዳ የሚገኙ የተለያዩ ተሽከርካሪዎች እና ሞተር ሳይክሎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈለጋል – test3.diretenders.com

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ ንብረትነቱ የተለያዩ የኦሮሚያ መ/ቤቶች ከአገልግሎት ውጭ የሆኑ በቢሮ፤ ዞን፤ ከተማና ወረዳ የሚገኙ የተለያዩ ተሽከርካሪዎች እና ሞተር ሳይክሎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈለጋል


Addis Zemen (Apr 25, 2026)

ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ግልጽ የሽያጭ

ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 10/2018

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ ንብረትነቱ የተለያዩ የኦሮሚያ መ/ቤቶች ከአገልግሎት ውጭ የሆኑ በቢሮ፣ ዞን፣ ከተማና ወረዳ የሚገኙ የተለያዩ ተሽከርካሪዎች እና ሞተር ሳይክሎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈለጋል።

ስለዚህ በጨረታዉ ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ግንቦት 13/2018 ዓ.ም ድረስ ሰነዱን መግዛት የምትችሉ ሲሆን፤

1. የኤጀንሲው አድራሻ፤ አዲስ አበባ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ ባልቻ ሆስፒታል ጀርባ/ የኢትዮጵያ ፖሊስ ሆስፒታል ፊትለፊት/ ጨፌ አናኒ ህንጻ ከሚገኘዉ የኤጀንሲው የግዢ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት 3ኛ ፎቅ (3rd Floor) ቢሮ ቁጥር-03 በመቅረብ የማይመለስ ብር 400.00 /አራት መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል የጨረታ ሠነዱን ከመንግስት ንብረት ዋጋ ግምትና ሽያጭ ዳይሬክቶሬት 3ኛ ፎቅ (3rd Floor) ቢሮ ቁጥር – 02 መግዛት ይችላሉ።

2. የጨረታ ሰነዱን መግዛት የሚቻለው ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30–6፡30 እና ከሰዓት በኋላ ከ7፡30 – 10፡30 ሰዓት ብቻ ነው።

3. የንብረቶቹን ሁኔታ እስከ ግንቦት 13/2018 ዓ.ም ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30–6፡30 ሰዓት እና ከሰዓት በኋላ ከ7፡30–10፡30 ሰዓት ድረስ በጨረታ ሠነዱ ላይ በተገለፀው ቦታ በመገኘት ማየት ይችላሉ።

4. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ግንቦት 14/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡ዐዐ ድረስ በኤጀንሲው ጽ/ቤት ለጨረታው በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

5. ጨረታው ግንቦት 14/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ5፡00 ተዘግቶ በዕለቱ በ5፡15 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።

5. ተጫራቾች ለያንዳንዱ ጨረታ መናሻ ዋጋ 20% /ሃያ ከመቶ/ የጨረታ ማስከበሪያ CPO የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ በማዘጋጀትና ከዋጋ ማቅረቢያው ኤንቨሎፕ ውስጥ በመክተት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

7. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

CPO ለማሰራት

የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ

Oromia Public Procurement & Property Disposal Agency

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 011-11 557-7027

የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ ፊንፊኔ


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *