Addis Zemen (May 05, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ኢኤአ–ባሪ/ግብጨ/012/2018
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የባሕር ዳር ሪጅን ከዚህ በታች የተገለጹትን አገልግሎት የማይሰጡ የተለያዩ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታ እና ቦታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
|
ሎት |
የዕቃው ዓይነት |
የጨረታ ማስከበሪያ |
የጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰዓት |
የጨረታ መክፈቻ ቀንና ሰዓት |
|
1 |
ብረታ ብረቶች (ለፋብሪካዎች ብቻ) |
75,000.00 |
ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም 8፡00 ሰዓት |
ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም 8፡30 ሰዓት |
|
2 |
የተሽከርካሪ ጎማ |
25,000.00 |
||
|
3 |
የተበላሹ ትራንስፎርመሮች |
75,000.00 |
ስለሆነም በጨረታው መካፈል የሚፈልግ ድርጅት ወይም ግለሰብ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ነጥቦች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ።
1. ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት ባሕር ዳር በሚገኘው በሪጅኑ ዋና መ/ቤት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ– ክርስቲያን ፊት ለፊት በሚገኘው ሕንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 408 በመምጣት ለአንዱ ሎት ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ።
2. ተጫራቾች ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት እንዲሁም ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 7፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ንብረቱ በሚገኝበት ቦታ በመሄድ መመልከት ይችላሉ።
3. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን በባንክ በተረጋገጠ (CPO) ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Bid Security) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ በድጋፍ ደብዳቤ የሚመጡ ተጫራቾችን አናስተናግድም።
4.ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ጨረታ ቁጥሩን በመግለጽ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
5. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህሕዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሰፕላይ ቼይን፣ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ ቁጥር 408 ይከፈታል።
6. ተጨማሪ ማብራሪያ ቢያስፈልግዎ በስልክ ቁጥር 058-320-6999 / 6775 መደወል ይችላሉ።
7. ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባሕር ዳር ሪጅን