Addis Zemen (May 11, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት
- ያገለገሉ የቢሮ እቃዎች ፤
- የመኪና ተመላሽ እቃዎች
- ያገለገሉ የእርሻ መሳሪያዎች ያገለገሉ፣
- ሞተር ሳይክሎች ፤
- ያገለገሉ ፒካፕ ደብል ጋቢና መኪና በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች የማይመለስ ብር 300/ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከአበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት መወሰድ ትችላላችሁ::
- ተጫራቾች ከዘመኑ የታደሰ የንግድ ህጋዊ ፍቃድ የምስክር ወረቀት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ::
- ያገለገሉ የቢሮ እቃዎች፣ የመኪና ተመላሽ እቃዎች፣ ያገለገሉ የእርሻ መሳሪያዎች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 3000 /ሶስት ሺህ ብር/ ከባንክ በተረጋገጠ ቼክ / ሲፒኦ /በማያያዝ ያገለገሉ ሞተር ሳይክሎች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 5000 /አምስት ሺህ ብር ከባንክ በተረጋገጠ ቼክ /ሲፒኦ /በማያያዝ ያገለገሉ ፒካፕ ደብል ጋቢና መኪና የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 30000 /ሰላሳ ሺህ ብር/ ከባንክ በተረጋገጠ ቼክ /ሲፒኦ/በማያያዝ ጨረታው የሚከፈተው ማስታውቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ይቆይና በ11 ኛው ቀን 8:00 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
ማሳሰቢያ–
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ ወደሚቀጥለው የስራ ቀን ይዘዋወራል፡፡
- ወረዳው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ከዘመኑ የታደሰ የንግድ ህጋዊ ፍቃድ የምስክር ወረቀት ማስረጃ መቅረብ የሚችሉ ቢባልም ማንኛውም ግለሰብ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
በተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር 0113302079 / ደውለው ማነጋገር ይችላሉ ::
በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት