በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ያገለገሉ የቢሮ እቃዎች፤ የመኪና ተመላሽ እቃዎች፣ ያገለገሉ የእርሻ መሳሪያዎች፣ ያገለገሉ ሞተር ሳይክሎች፤ ያገለገሉ ፒካፕ ደብል ጋቢና መኪና በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል – test3.diretenders.com

በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ያገለገሉ የቢሮ እቃዎች፤ የመኪና ተመላሽ እቃዎች፣ ያገለገሉ የእርሻ መሳሪያዎች፣ ያገለገሉ ሞተር ሳይክሎች፤ ያገለገሉ ፒካፕ ደብል ጋቢና መኪና በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል


Addis Zemen (May 11, 2026)

የጨረታ ማስታወቂያ

በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ /ቤት

  • ያገለገሉ የቢሮ እቃዎች
  • የመኪና ተመላሽ እቃዎች
  • ያገለገሉ የእርሻ መሳሪያዎች ያገለገሉ፣
  •  ሞተር ሳይክሎች
  • ያገለገሉ ፒካፕ ደብል ጋቢና መኪና በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡

ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች የማይመለስ ብር 300/ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከአበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ /ቤት መወሰድ ትችላላችሁ::

  • ተጫራቾች ከዘመኑ የታደሰ የንግድ ህጋዊ ፍቃድ የምስክር ወረቀት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ::
  • ያገለገሉ የቢሮ እቃዎች፣ የመኪና ተመላሽ እቃዎች፣ ያገለገሉ የእርሻ መሳሪያዎች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 3000 /ሶስት ሺህ ብር/ ከባንክ በተረጋገጠ ቼክ / ሲፒኦ /በማያያዝ ያገለገሉ ሞተር ሳይክሎች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 5000 /አምስት ሺህ ብር ከባንክ በተረጋገጠ ቼክ /ሲፒኦ /በማያያዝ ያገለገሉ ፒካፕ ደብል ጋቢና መኪና የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 30000 /ሰላሳ ሺህ ብር/ ከባንክ በተረጋገጠ ቼክ /ሲፒኦ/በማያያዝ ጨረታው የሚከፈተው ማስታውቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ይቆይና 11 ኛው ቀን 8:00 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 830 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡

ማሳሰቢያ

  1.  ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ ወደሚቀጥለው የስራ ቀን ይዘዋወራል፡፡
  2.  ወረዳው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  3.  ከዘመኑ የታደሰ የንግድ ህጋዊ ፍቃድ የምስክር ወረቀት ማስረጃ መቅረብ የሚችሉ ቢባልም ማንኛውም ግለሰብ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡

በተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር 0113302079 / ደውለው ማነጋገር ይችላሉ ::

በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ /ቤት