የትምህርት መሣሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት ባለ 20 ጫማ ብዛታቸው 03 /ሶስት/ ኮንቴነሮችን ባሉበት ይዞታ ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል – test3.diretenders.com

የትምህርት መሣሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት ባለ 20 ጫማ ብዛታቸው 03 /ሶስት/ ኮንቴነሮችን ባሉበት ይዞታ ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል


Addis Zemen (Jul 22, 2026)

የኮንቴነር ሽያጭ ጨረታ ማስታሠቂያ

የትምህርት መሣሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት ባለ 20 ጫማ ብዛታቸው 03 /ሶስት/ ኮንቴነሮችን ባሉበት ይዞታ ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።

በዚሁ መሠረት ተጫራቾች

  • የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የቫት እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን ሠርተፍኬት ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለሰ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ገዝተው ዝርዝሩን ከሰነዱ መመልከት የሚችሉ ሲሆን የጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) በባንክ የተመሰከረለት CPO ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ሰነዱን በመግዛት ንብረቶቹ በሚገኙበት በሃዋሳ ከተማ /ከተማ ባህል አዳራሽ ምስራቅ ጮራ 2ተኛ ደረጃ /ቤት በመገኘት ማየት ይችላሉ።
  • ጨረታው 11ኛው ቀን ከረፋዱ 400 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት 430 ሰዓት ተራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ ዋና /ቤት ይከፈታል። ሆኖም የጨረታው መክፈቻ ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም ዝግ ላይ ከዋለ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
  • ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቶ የተጠበቀ ነው።

የድርጅቱ ዋና /ቤት አድራሻ / ቦሌ ክፍለ ከተማ ከመገናኛ ወደ ጉርድ ሾላ በሚወስደው መንገድ ከሆሊ ሲቲ ሴንተር ህንፃ ወደ ቀኝ ILRI እና FOA ድርጅቶች መካከል በሚያስገባው መንገድ ገባ ብሎ በሃዋሳ ከተማ /ከተማ ባህል አዳራሽ ምስራቅ ጮራ 2ተኛ ደረጃ /ቤት ይገኛል።

ለበለጠ መረጃበሥራ ሰዓት አዲስ አበባ 09 11 04 32 12 ወይም 09 11 86 61 67 ሃዋሳ 09 35 35 35 49 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።

የትምህርት መሣሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *