Addis Zemen (Aug 17, 2026)
የሽያጭ የጨረታ ቁጥር ግልፅ /ኦኮኮ-002/2018 ዓ/ም
የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ለአገልግሎት የማይጠቀምበትን የተለያዩ ያገለገሉ የመኪና መለዋወጫ ዕቃዎችን “Spare Parts”፣ ያገለገሉ ጎማዎች፣ ባትሪዎች፣ የተለያዩ ቁርጥራጭ ብረቶችን (scraps) ፣ ያገለገሉ የፕላስቲክ እና የብረት በርሜሎችን Barrels”፣ የተለያዩ “Auxiliaries, Mixer, Compressor, Generator, Dewatering Pump, water pump, Vibrator’ የተለያዩ የቢሮ ዕቃዎችን “computer, Laptop, Printer, scanner, TV and Furniture” ያገለገለገሉ የተለያዩ የግንባታ ዕቃዎች “Construction materials, Aluminum door and plastic door” የሆኑትን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
- ተጫራቾች ሰነድ ለመግዛት ሲመጡ ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ ይዞ በመምጣት የንብረቶቹን ዝርዝር መረጃ የያዘ ፣ የተጫራቾች መመሪያ እና ዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ ቃሊቲ ከመካኒኮች ማሰልጠኛ ፊት ለፊት ካለው መ/ቤታችን 1ኛ ፎቅ ከኮርፖሬት ግዢ ክፍል በመቅረብ የማይመለስ ብር 1,000.00 /አንድ ሺህ / ከፍለው መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚገዙትን ንብረት ባቀረቡት ጠቅላላ ዋጋ 20 በመቶ (20 %) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል
- የጨረታ የመገምገሚያ መስፈርት፣ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ሲፒኦ/ እንዲሁም በሰነዱ የተገለፁትን አሟልቶ መገኘት ይኖርባቸዋል።
- ለዕቃዎቹ የቀረቡትን ዋጋ 20 በመቶ (20%) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ያላስያዘ እና በሰነዱ የተቀመጡትን ሌሎች ነጥቦችን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውድቅ ይደረጋል።
- የሚቀርበው የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ከፊንፊኔ ውጪ ከሆነ ከኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ብቻ ይሆናል።
- ተጫራቾች ሰነድን ገዝቶ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከሰኞ እስከ ዓርብ ከጠዋቱ 3፡00 እስከ ከሰዓት 10፡30 ባለው ጊዜ ውስጥ ንብረቶቹን ባሉበት ቦታ ፊንፊኔ ዋና ቢሮ፣ አለምገና ፣ ጉደር አምቦ፣ ነቀምቴ ፣ ሀረር፣ መቱ ፣ ጅማ ፣አርጆ ፣ባሌ ሮቤ ፣ወልመል ፕሮጀክት፣ዱከም ክሬሸር ፣አዳማ 03፣ አዳማ ዋና ቢሮ፣ አዳማ ብሎኬት ማምረቻ፣ ወለንጪቲ ቦፋ ፣ ጨለጨል፣ ፊንፊኔ ጋራጅ፣ ጎሎልቻ፣ አሰላ አርሲ ዬኒቨርስቲ ፣ ሻሻመኔ፣ ሱሉልታ፣ ገላን ሰልቫጅ መጋዘን፣ገላን ድሪሊንግ በመሄድ በስራ ሰዓት መመልከት ይችላሉ
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ንብረት ዋጋ ድርጅቱ ባዘጋጀው የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ በኦርጅናል ላይ በመሙላት በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ እስከ ጳጉሜ 3/2018 ዓ.ም ከጠዋት 5፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ተወካዮች በተገኙበት በዚሁ ዕለት 5፡30 ላይ የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ኦዳ አደራሽ ውስጥ ይከፈታል። ተጫራቹ በራሱ ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኝ ቢቀር ጨረታውን ከመከፈት አያስተጋጉልም።
- በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ማሸነፋቸው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ገንዘብ ገቢ በማድረግ ንብረቱን መረከብ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህ ካልሆነ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ለኮርፖርሸኑ ገቢ ሆኖ ከጨረታው ይሰረዛል።
- የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ያወጣውን ጨረታ ሰነድ ሳይገዛ የተወዳደረ ማንኛውም ተጫራች ከተገኘ ከውድድር ውድቅ ይደረጋል።
- ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 09-11-94-01-71/0911–42-84-06 ደውሎ መጠየቅ ይችላል።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው።
የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን