Reporter (Jul 01, 2026)
ከህንፃ ግንባታ የተረፉ የግንባታ ግብዓት እቃዎችን ለመሸጥ
የጨረታ ቁጥር 003/2018
ፀደይ ባንክ አ.ማ በደቡብ ጎንደር እስቴ ከተማ የሚገኙ ከህንፃ ግንባታ የተረፉ የግንባታ ግብዓት እቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ስለሆነም ከዚህ በታች የቀረበውን የጨረታ መመሪያ የሚያሟላ ማንኛውም ፍላጎት ያለው ግለስብ /ድርጅት/ መወዳደር የሚችል መሆኑን እንገልጻለን።
1. በረታው በሁሉም አይነት ወይም በከፊል መወዳደር ይቻላል።
2 የግንባታ ዕቃዎቹን በስራ ሰዓት ደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ ከተማ በሚገኘው ፀደይ ባንክ ቅ/ፅ/ቤት በመገኘት የጨረታ ሰነድ ከገዙበት ቀን ጀምሮ ማየት ይችላሉ::
3. ተጫራቾች የሚገዙበትን ጠቅላላ ዋጋ በጨረታ ስነዱ በተቀመጠው የዋጋ ፎርማት ላይ መሙላት ይኖርባቸዋል:: በነጠላ ዋጋና በጠቅላላ ዋጋ ላይ ልዩነት ካለ ነጠላ ዋጋው የሚያዝ ይሆናል:: ዋጋ ሲሞላ ስርዝ ካለ ፊርማ ሊኖረው ይገባል:: ሆኖም ግን ስርዝ ድልዝ ከበዛበትና ግልፀኝነት ከጐደለው ተወዳዳሪው ከጨረታው ይሰረዛል::
4 ለጨረታ ማስከበሪያ የአጠቃላይ ዋጋውን 2% በሲፒኦ/CPO/ ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ የ90 ቀን በፀደይ ባንክ አማ ስም ማሰራት ይኖርባቸዋል:: ከየትኛውም የፀደይ ባንክ አማ ቅርንጫፍ የተስጠ ሲፒኦም ሆነ ባንክ ጋራንቲ ተቀባይነት የለውም::
5. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ ባሉት የስራ ቀኖች ማለትም ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት እስከ 6:00 ሰዓት እና ከሰዓት በኋላ ከ7:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 11:00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት እስከ 6:00 ሰዓት የማይመለስ ሁለት መቶ ብር /200.00/ ፀደይ ባንክ ለገሃር ቅርንጫፍ ወይም በማንኛውም የፀደይ ባንክ ቅርንጫፍ በመክፈል ሰንጋተራ አካባቢ ጤና ሚኒስቴር ዝቅብሎ ከሚገኘው የባንኩ ዋና መ/ቤት 16ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 09 ከግዥ ክፍል ሰነዱን መዉሰድ ይችላሉ::
6. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የጨረታ ሰነድ በሰም በታሸገ ፖስታ እስከ ሐምሌ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ አዲስ አበባ ሰንጋተራ አካባቢ በሚገኘው ፀደይ ባንክ ዋና መ/ቤት 16ተኛ ፎቅ ግዥና ዉል አስተዳደር ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል:: ጨረታው በዚሁ እለት በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመስሪያ ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል::
7. የጨረታዉ መዝጊያ ሰዓት ካለፈ በኋላ የሚመጣ ማንኛዉም የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት አይኖረዉም::
8. ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ፀደይ ባንክ አ.ማ.