Reporter (Aug 09, 2026)
ያገለገሉ ካውንተር እና ኬጅ ሽያጭ ጨረታ
የማስታወቂያ ቁጥር፡ ዓባይ 02-2026-27
የዓባይ ባንክ አ.ማ በአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጪ በሚገኙ ቅርንጫፎች የሚገኙ ያገለገሉ ካውንተር እና ኬጅ ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ስለሆነም፡–
1.ተጫራቾች የጨረት ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 / ሁለት መቶ ብር ብቻ/ በዓባይ ባንክ ዓብይ ቅርንጫፍ በመክፈልና ደረሰኙን በመያዝ ባምቢስ ኖክ ማደያ ፊት ለፊት በሚገኘው ዝቋላ ኮምፕሌክስ 8ኛ ፎቅ ከግዥና ንብረት አስተዳደር ዲፓርትመንት ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ዘወትር በስራ ስዓት ከሰኞ እስከ አርብ ጠዋት 2፡00- 6፡00፣ ከስዓት በኋላ ከ7፡00-11፡00 እንዲሁም ቅዳሜ ጠዋት 2፡00-6፡00 ማግኘት ይችላሉ።
2. ተጫራቾች የሚጫረቱትን የካውንተር እና ኬጅ የሚገዙበትን የአንድ ሜትር ሊንየር (እርዝመት) ዋጋ በመሙላት በሰም በታሸገ ኤቨሎፕ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ድረስ በባንኩ ዋና መ/ቤት ባምቢስ ኖክ ማደያ ፊት ለፊት ዝቋላ ኮምፕሌክስ 8ኛ ፎቅ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዲፓርትመንት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
3. ጨረታው ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተዘግቶ በዚያው ዕለት 9፡00 ሰዓት በተጫራቾች ወይም ተወካዮች በተገኙበት ይከፈታል።
4. ተጫራቾች ለጨረታ ማስያዥያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (C.P.O) ለጨረታ ማስከበሪያ 20,000 ብር ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
5.ተጫራቾች የሚጫረቱትን ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) 15% ጨምሮ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
6.ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር +251-11 557 1529 / +251-11 554 9741 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ።
“ዓባይ– የታላቅነት ምንጭ!!”